Friday, May 04, 2018

የአባቶች ውሳኔና መግለጫ


የአባቶች ውሳኔና መግለጫ መስጠት ሰዎችን ከስሕተት ያድናል፦ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ/ክ ትጠብቁዋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ ከሄድሁ በኁዋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኁዋላ ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካክላችሁ እንደሚነሡ እኔ አውቃለሁ ይላል ስለዚህ በጠቅላይ ቤተክህነት በሀገረ ስብከት በወረዳ በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እንደተዋረዱ በየደረጃው የሚፈቱ ችግሮች ውሳኔ አግኝተው መግለጫ ቢሰጥ ሁሉም ነገር ግልጽ ይሆናል ከታች እስከላይ ስብሰባ ይካሄዳል ነገሮች ይጀመራሉ መፍትሄ ግን የለም ለምን ምዕመናንን የሚጎዱ ነገገሮች ሲከናወኑ እያወቅን በጥቅማጥቅም የምንዳለለው ለምንድነው ለምሳሌ በአዲስ አበባ ከተማ ዙረያ




ጠንቁዋይዎች የባንዲራ ቀለም ቤታቸውን ቀብተው የቤተ ክርስቲያንዋን ጉልላት ሲያሰቀምጡ ዝም ለምን 2ኛ በሰሜን ሸዋ ደራ የገብረ ክርስቶስ ገዳም ገድሜአለሁ ጠበል አፍልቄአለሁ እያለች አንዲት ሴት ዛር ያደረባት ለራስዋ እየተሰቃየች ለሰዎች ግንባራቸውን እያነበበች ስትጠነቁል ዝም ለምን መነገጃ ሆነ 3ኛ በአዲስ ዓለም ማርያም ገዳም አንዲት መነኩሴ እማሆይ ተነስተው በሌላ ሰው መንፈስ አጋንት እየሳቡ በጥንቆላ መንፈስ ሲአናግሩ ዝም ለምን ሌላው የሱዳን መተት እጽ እየረጩ ጋኔል እያስጮሁ እንፈውሳለን እያሉ ቤተ ክርስቲያን ገብተው ሲአጠምቁ ገንዘብ ይሰበስቡልናል በማለት ዝም ጥቅሙ ሲጎድል መጣላት ለምዕመናን ምንጥቅም ይሰጣል ውድ አባቶቼና ወገኖቼ እዳ አለብን ድርሻችንን እንወጣ በየደረጃው ግምገማ ይካሄድ በቤተ/ክ መነገድ ይበቃል የማቴ ም7ቁ21 የሐዋ ሥራ ም20ቁ28 ይ መ ከሊቀ/ትጉ/መር/ ገ/መስቀል ኃ/መስቀል ከቀጨኔ



No comments:

Post a Comment