Monday, April 23, 2018

ስለ ማህበራችን አጭር መግለጫ

ስለ ማህበራችን አጭር መግለጫ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ውድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታይዎችና አራማጆች እንደምን አላችሁ እግዚአብሔር ይመስገን የሃይማኖት እውቀት ማስፋፍያ ማህበር ወይም በአጭሩ የእማማ ማህበር የዛሬ 33 ዓመት በሰሜን ሸዋ ቡልጋ ውስጥ በሊቀ ትጉ ባሕታዊ /መስቀል /መስቀል መስከረም 12ቀን 1979 ተመሰረተ አላማው ወንጌል መስበክ ድሆችን መርዳት የገጠር ቤተ እና ገዳማትን ማገዝ ለሀገር ለወገን ምሕላ ጸሎት ማድረስ በንስሐ ቄደር እያስጠመቁ ሰዎችን ለንስሐ ማብቃት ዋና ዋና ተግባሩ ነው በመላው ዓለም የሚገኜው ማህበራችን በጎ ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎችን ምርጫ ይሰጣል እድሜ ልክ አባል ለመሆን አንድ ጊዜ 10 000ብር የክር አባል በየወሩ 100ብር ቁዋሚ አባል ለመሆን በየወሩ 5ብር በመክፈል


በአሉበት ሀገር ሆነው አባል ይሆናሉ መታወቂያ ይሰጣቸዋል በቢሮ በደረሰኝ በውጭ ከሆነ በባንክ ይከፍላሉ ሊላው አገልግልት ለመስጠት በገንዘብና በማቴርያል የሚረዱ ፍኖተ አብርሃም ይባላሉ በኮሚቴነት ገብተው የሚአገለግሉ አርድዕት ይባላሉ በአላቸው ሙያ የሚአገለግሉ የሙያተኞች ሕብረት ይባላሉ እንደየፍላጎታቸው መመዝገብ ይኖርባቸዋል ይህ ማህበር መለያየትንና የሰው ስም ማጥፋትን አጥብቆ ያወግዛል በቤተክህነ በመንግስት ሕጋዊ ፈቃድ የተሰጠው ማህበር ነው እንዲህ በአዲሰ አበባ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ አጠገብ ምዕራፈ ቅዱሳን የሰገነት ኪዳነምሕረትና አቡነ ዜና ማርቆስ ቤተጸሎት እንገኛለን በፎርሙላይ ሙሉ ስምዎትንና አድራሻዎትን በመሙላት የማህበሩ አባል ይሁኑ ለበለጠ መረጃ 0920744622 0925083599 0911877059 23430 መጻፍ ይችላሉ ሰፊ የቪዲዮ መረጃና ትምህርት መምህር መስቀል በሚል ገብታችሁ የዕማማ ኢትዩብ ተመልከቱ ብዙ መከራ አሳልፎ ከዚህ የደረሰ ማህበር ነው መልዕክቱን ስለአነበባችሁ አመሰግናለሁ ሊቀ ትጉ /መስቀል /መሰቀል ነኝ የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም ምልጃና ጸሎት አይለየን አሜን።

No comments:

Post a Comment