Tuesday, August 21, 2018

የቅኔ ትንቢት ‹‹ሱ››



ቅ/ሥላሴን አንግሱ እንድትወደሱ በመቅደሱ፤
ቅዳሴው ውዳሴው እንዲያርግ ወደእርሱ፤
በጣም ደስይላል የተስተካከለው መቅደሱ፤
ይህንን ለማየት ያዘናችሁ አሁን ደስይበላችሁ በእርሱ፤
በጣም ያምራል የወደፊት መቅደሱ በእርሱ፤
በሀገር መውደድ ገስግሱ እንዳትልከሰከሱ፤
በሃይማት ቁሙ በዘላለም ሕይወት እንድትቀደሱ፤
የሥላሴን ሚስጢር አወድሱ  እንዲመሰገን በመቅደሱ፤
ቅዳሴው ይሰምራል ሲጸዳ መቅደሱ በእርሱ፤
በፍቅር መንገድ ገስግሱ ከላይ ነው እርሱ፤
እንዲሸነፍ ጠላታችን በሃይማት ጎልምሱ፤
              አሁን ጥሩነው የሃይማኖት መቅደሱ አንድ ሆነ በእርሱ፤
              የቀራችሁም ተመልሳችሁ ተቀደሱ በእርሱ፤
              ፀሐይ ይወጣል በመቅደሱ እንድትታደሱ፤
              ሀገር ይስተካከላል በመጥረጊያ ንፋሱ እንዳትተራመሱ፤
              ምእመናን እግዚአብሔርን አንግሱ በመቅደሱ ፤
                                                     ነሐሴ 14 ቀን 2010 ዓ.ም
                                                  ከእግዚአብሔር ባሪያና አገልጋይ
                                                 ከሊቀ ትጉ መ/ር ገ/መስቀል ኃ/መስቀል ቀጨኔ

No comments:

Post a Comment