ወገብረ
ሰላመ በደመ
መስቀሉ <<በመስቀሉ
ላይ በፈሰሰው ደሙ ሰላምን አደረገ>> ቆላ. 1-፡-20
መስቀል በቀደመ ዘመን ለኃጢአተኞች እግዚአብሔርን ለበደሉ መቅጫ የነበረ ነው፡፡ በእንጨት ላይ
የተሰቀለም በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና፡፡ ኦ/ዘዳ 21፡23 በሐዲስ ኪዳን ግን ለክርስቲያኖች ኃይል ጽንዕ ቤዛና መድኃኒተ ነፍስ ሆኖ የሚያገለግል ዓርማ ነው፡፡ መስቀል የምንለው
በቁሙ ከቤተክርስቲያን ጉልላት እስከ ምዕመናን ንቅሳት የሚታይ የድል ምልክት የደህንነት ዓርማ (ምልክት) የክርስቲያኖች የማንነት
መገለጫ የተጋድሎ ፍኖት ነው፡፡ 1ጴጥ. 2፡21
የክርስቶስ መስቀል ለምናምን ለኛ ፡- የጥል ግድግዳ የፈረሰበት ሰላማችን ነው ኤፌ 2፡14 ሰው እንጨት ቆርጦ ቢበላ አምላኩን በደለ የፀብ ግድግዳም ተተከለ ሰው ከአምላኩ ተለየ፡፡ ‹‹ለያይቶን የነበረውን የጥል ግድግዳ ያፈረሰና አይሁዳዊያንና አሕዛብን አንድ ያደረገ ሰላማችን ክርስቶስ ነው›› እንዲል: : ከእርሱ ጋር የታረቅንበት ኃይላችን ነው በመስቀል ላይ በመሞት ጠላትን አስወገደ ሁለቱንም አንድ አካል አድርጎ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ እንዲል ኤፌ. 2፡16 ጠላታችን የራቀበት እኛ የቀረብንበት ጋሻችን ነው፡፡ የቀደመው እባብ የዲያብሎስን ራስ የተቀጠቀበት እኛም ድል መንሳትን በግለጥ ያየንበት ዕፀ መድኃኒት ነው፡፡ በእኛ የነበረውን የሚቃወመንንም በትዕዛዛት የተፃፈውን የዕዳ ደበዳቤ ፅሕፈት ደመሰሰው እርሱንም በመስቀሉ ቸንክሮ ከመንገድ አስወገደው እንዲል ቆላ. 2፡14 ዐረፍተ ማዕከል የተናደበት የሕይወት ህብስት የተቆረሰበት ዕፀ መስቀል በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት በዓለ መስቀልን መከበር የተጀመረው ዛሬም በኢትዮጵያችንም በተለይ በግሸን ደብረ ከርቤ ከአራቱ ማዕዘን በሚመጡ ምዕመናን በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል:: መስቀል በዓመት አምስት ጊዜ የሚከበር ሲሆን ይኸውም መስከረም 16 ቀን የደመራ በዓል ቅዳሴ ቤት መስከረም 17 ቀን ንግስት ዕሌኒ ቁፋሮ ያስጀመረችበት መስከረም 10 ቀን አፄ ዳዊት መስቀሉን የተረከቡበት አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በደብረ ብርሃን ከተማ ያስገቡበት ተቀፀል ጽጌ ይባላል፡፡ መስከረም 21 ቀን 1446 ዓ.ም በግሸን ተራራ ያረፈበት በማስመልከት በየዓመቱ እየታሰበ ይገኛል፡፡ በረከተ መስቀሉ አይለየን!
የክርስቶስ መስቀል ለምናምን ለኛ ፡- የጥል ግድግዳ የፈረሰበት ሰላማችን ነው ኤፌ 2፡14 ሰው እንጨት ቆርጦ ቢበላ አምላኩን በደለ የፀብ ግድግዳም ተተከለ ሰው ከአምላኩ ተለየ፡፡ ‹‹ለያይቶን የነበረውን የጥል ግድግዳ ያፈረሰና አይሁዳዊያንና አሕዛብን አንድ ያደረገ ሰላማችን ክርስቶስ ነው›› እንዲል: : ከእርሱ ጋር የታረቅንበት ኃይላችን ነው በመስቀል ላይ በመሞት ጠላትን አስወገደ ሁለቱንም አንድ አካል አድርጎ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ እንዲል ኤፌ. 2፡16 ጠላታችን የራቀበት እኛ የቀረብንበት ጋሻችን ነው፡፡ የቀደመው እባብ የዲያብሎስን ራስ የተቀጠቀበት እኛም ድል መንሳትን በግለጥ ያየንበት ዕፀ መድኃኒት ነው፡፡ በእኛ የነበረውን የሚቃወመንንም በትዕዛዛት የተፃፈውን የዕዳ ደበዳቤ ፅሕፈት ደመሰሰው እርሱንም በመስቀሉ ቸንክሮ ከመንገድ አስወገደው እንዲል ቆላ. 2፡14 ዐረፍተ ማዕከል የተናደበት የሕይወት ህብስት የተቆረሰበት ዕፀ መስቀል በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት በዓለ መስቀልን መከበር የተጀመረው ዛሬም በኢትዮጵያችንም በተለይ በግሸን ደብረ ከርቤ ከአራቱ ማዕዘን በሚመጡ ምዕመናን በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል:: መስቀል በዓመት አምስት ጊዜ የሚከበር ሲሆን ይኸውም መስከረም 16 ቀን የደመራ በዓል ቅዳሴ ቤት መስከረም 17 ቀን ንግስት ዕሌኒ ቁፋሮ ያስጀመረችበት መስከረም 10 ቀን አፄ ዳዊት መስቀሉን የተረከቡበት አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በደብረ ብርሃን ከተማ ያስገቡበት ተቀፀል ጽጌ ይባላል፡፡ መስከረም 21 ቀን 1446 ዓ.ም በግሸን ተራራ ያረፈበት በማስመልከት በየዓመቱ እየታሰበ ይገኛል፡፡ በረከተ መስቀሉ አይለየን!
አድራሻ፡- ከቀጨኔ መድኃኒዓለም ቤተ/ክ ዝቅ ብሎ ያገኙናል
በም.ቅዱ.የሰገነት ኪዳነምሕረት
ቤተ ጸሎት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ
ለበለጠ መረጃ፡-
0911-877059 / 0111-572581 / 0920-744622 ጉ/ክ/ከተማ አ.አ. ኢትዮጵያ