Wednesday, February 26, 2020

ጾመ ኢየሱስ

ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾው ጾም ‹‹ጾመ ኢየሱስ›› ይባላል፡፡
  • ጾም ‹‹ጾመ ጦመ›› ከሚል የግእዝ ግሥ የወጣ ሲሆን፣ ጾመ ማለት እህል ውሃ ሳይቀምስ   ዋለ፣ ሥጋ ከቅቤ ተከለከለ ማለት ነው፡፡(ትን. ዳን 10÷3)
  • ጸም ጦም ማለት ሲሆን ጊዜ ሳይደርስ እንዳይበላ፣ እዳይጠጣ የሚከለክል ሕግ በቅዱስ መጽሐፍ የታዘዘ የጸሎት ወንድም ማለት ነው፡፡ (ተን. ኢዩ 1÷14፣ 2÷15)
  • ጾም ቤሌላ አነጋገር ልጓም ይባላል፡፡ ይህም ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓ መጽሐፉ ‹‹ጾም ልጓም ፍሬሐ ጥዑም ትሕተ ኢናምስላ ለጾም ትርጉም ጾም ልጓም ናት ፍሬዋም ጣፋጭ ነው ጾምን የተናቀች አናድርጋት (ጾመ ድጓ) ከሚለው የተወሰደ ነው፡፡ ልጓም የሰም አነጋገር ሲሆን ጾም ወርቅ ነው፡፡ ጾም ልጓም ናት ማለቱ በልጓም ፈረሶች ይገታሉ በጾምም የሰው ልጅ ሰውነቱን ከኀጢያት ሥራ ይገታበታልና፡፡ ፍሬዋም ጣፋጭ ነው ማለቱ ጹመን የምናገኘውን ክብር መግለጡ ነው፡፡ ስለ ጾም ባጭሩ ይህንን ካልን ስለ ጾመ ኢየሱስ እንቀጥላለን፡፡
             ጾመ ኢየሱስ የተለያዩ ስሞች አሉት
1. ጾመ ኢየሱስ ይባላል

         ጾመ ኢየሱስ የተባለበት ምክንያት ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኃላ ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሄዶ በዚያ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከዘረጋ ሳያጥፍ ከቆመ ሳይቀመጥ እሱ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ከርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ ነው፡፡