የዓብይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት
- ምኩራብ ማለት የአይሁድ መቅደስ፣ ቤተ ጸሎት እንዲሁም ታላቅ አዳራሽ ማለት ሲሆን ለአምልኮና ለትህምህርት መማሪያ ይገለገሉበት ነበር፡፡ ምኩራብ በአለቆች ይመራ ነበር፡፡ (ማር 5÷22፣ ዮሐ 3÷14-15,18÷8) በእየሳምንቱ ሕዝቡ ሁሉ በምኩራብ ይሰበሰቡ ነበር (ሉቃስ 4÷16፣ የሐ.ሥ 15÷21) ወንዶችና ሴቶች ለእየብቻቸው ይፀልዩና ይቆሙ እንዲሁም ይቀመጡ ነበር፡፡
- ታዲያ ይህ ሳምንት ለምን ምኩራብ ተባለ? ሲባል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምዋለ ስብከቱ ለማስተማር ወደ ምኩራብ ገብቶ ነበርና ለዚያ መታሰቢያ እንዲሆን ምኩራብ ተብሏል (ማቴ 4÷23፣ ማር 1÷21፣ ሉቃ 4÷15)