Tuesday, March 10, 2020

ምኩራብ


የዓብይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት
  •   ምኩራብ ማለት የአይሁድ መቅደስ፣ ቤተ ጸሎት እንዲሁም ታላቅ አዳራሽ ማለት ሲሆን ለአምልኮና ለትህምህርት መማሪያ ይገለገሉበት ነበር፡፡ ምኩራብ በአለቆች ይመራ ነበር፡፡ (ማር 5÷22፣ ዮሐ 3÷14-15,18÷8) በእየሳምንቱ ሕዝቡ ሁሉ በምኩራብ ይሰበሰቡ ነበር (ሉቃስ 4÷16፣ የሐ.ሥ 15÷21) ወንዶችና ሴቶች ለእየብቻቸው ይፀልዩና ይቆሙ እንዲሁም ይቀመጡ ነበር፡፡
  • ታዲያ ይህ ሳምንት ለምን ምኩራብ ተባለ? ሲባል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምዋለ ስብከቱ ለማስተማር ወደ ምኩራብ ገብቶ ነበርና ለዚያ መታሰቢያ እንዲሆን ምኩራብ ተብሏል (ማቴ 4÷23፣ ማር 1÷21፣ ሉቃ 4÷15)

ቅድስት


የዓቢይ ጾም ሁለተኛ ሣምንት ቅድስት ይባላል፡፡

  • ቅድስት ማለት የተቀደሰች፣ የተባረከች፣ ንጽሕት፣ ልዩ የተመሰገነች ማለት ነው፡፡
  • ቅድስት የተባለበት ምክንያት ‹‹ጾምን ቀድሱ ጉባኤውንም አውጁ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ (ኢዩ 1÷14) ብሎ በነቢዩ በኢዩኤል አድሮ የተናገረ ቅዱስ እግዚአብሔር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾማት ጾም ስለሆነች ቅድስት ትባላለች፡፡
  • እንዲሁም የዲያብሎስን ፈተና ድል ለመንሳት በቅድስት ከተማ በኢየሩሳሌም በሰሎሞን ቤተ መቅደስ ጫፍ የቆመባት ዕለት ሰው ጾምን ጾሞ እንደፈጣሪው ፈተናን ድል ነስቶ ቅድስናንና ክብርን ያገኛል፡፡ ለምን ብየ ቅድስቴን ጾምኳት እንዲሉ መጾም ቅድስናን ለማግኘት ነውና፡፡